Thursday, June 6, 2013

አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት

 
ECADF Statment regarding Addis Ababa's demonstration
ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-
1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣
 
2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በአባይ ጉዳይ ላይ ዛሬ ደግሞ…

 

 

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም
Prof. Mesfin Woldemariamጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም በሚያሰፈስፉበት ጊዜ በርቱ እያሉ የሚያቅራሩ ሞልተው ነበር፤ ዛሬ አቀራሪዎቹም ሆኑ ጀብደኖቹ በኤርትራ ጦርነት ያለቀባሪ ስለቀሩት ሰዎች፣ ጠዋሪ ስላጡ እናቶችና አባቶች፣ አሳዳጊ ስለሌላቸው ልጆችና አካለ-ጎደሎ ለሆኑት የሚያስብላቸው አለ ወይ? የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መነሣትና በኢጣልያ የግራዚያኒ ሐውልት እንዳይሠራ የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎ ለሰልፍ የወጡትን አስሮ ያሳደረ አገዛዝ ለአገራቸው ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ያሳያል፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ሲወዱ ራሳቸው በልጽገው ለልጆቻቸው ብልጽግናን እንዲያወርሱ ሕይወታቸውን ቢጠብቁ ለአገራቸውም ክብር ይሆናሉ፡፡