ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-
1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣
2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።