ለሁለት አስርተ አመታት በኢትዮጲያና በህዝቦቿ ላይ ነግሶ በማን አለብኝነት አድራጊ ፈጣሪ ሆኖ በሁሉም ያገሪቱ አቅጣጫዎች ሰላማዊውን ህዝብ ለሞትና ለስደት እንዲሁም ለእስር ሲዳርግ የነበረው አምባገነኑ የህውሃት ዘረኛ ቡድን የመለስ ዜናዊ ሞት ተከትሎ በይስሙላ ምርጫ ያስቀመጠው አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የዚሁ ዘረኛ ቡድን ደቀ መዝሙር ሆኖ በነሱ በመቃኘት ተፈጥሮአዊ ባህሬያቸውን ወርሶ አሁንም በሃገራችን ስርዓቱ ካለው እኩይ ተፈጥሯዊ ባህሪ አንፃር የናፈቅነውንና የተመኘነውን ነፃነትም ሆነ ለውጥ ሳይመጣ እነሆ ሌሎች ንፁሃን ሲገደሉና ሲሰደዱ እንዲሁም ሲታሰሩ አየን ሰማን፡፡
ለብዙሃን ዜጎች ህይወት መጥፋት፣ መሰደድና በየእስር ቤቱ መታጎር ተጠያቂ የሆነው አምባገነኑ የወያኔ ቡድን እንዲሁም ስርዓቱ በተለይ ሃገር ሲያፈርሱ፣ ሲመዘብሩና ደሃውን የህብረተሰብ ክፍል ሲየፈናቅሉና በችጋር ሲቆሉ የነበሩት የህወሃት መስራቾች በዘፈቀደ ባገኙት አጋጣሚ እዚህ ምስኪን ህዝብ ላይ አፋቸውን ማላቀቃቸውን መዘባበታቸው የተለመደ ቢሆንም የወያኔ ጠ/ሚንስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በተለያየ አጋጣሚ በስርዓቱ መገናኛ ቡዙሃን ቀርበው የሚሰጡት አስተያየትም ሆነ የሚናገሩት እጅግ የወረደና ስነምግባር የሌለው ዲስኩር ሰውየው በራሳቸው ሳይሆን ስርዓቱ እንደፈለገ እንደሚዘውራቸው ፍንትው አርጎ የሚያሳይ ነው፡፡