Sunday, March 9, 2014
የኢትዮጵያን ለኢትዮጵያ ወይም የወያኔን ለወያኔ
ሚሊዮን ሊማ ከኖርዌይ
በአንድ ወቅትአንድ ዘጋቢ የኢትዮጵያን ባንዲራ በሚመለከት ተዘዋውሮ ካናገራቸው የመዲናይቱ ነዋሪዎች አንዱ፥ “እኛ አገራችንን የምንወደው ወያኔዎች ስለነገሩን አይደለም። እሱማ ባንዲራችንን ባጥላሉበት ዘመንም አገራችንን እንወድ ነበር፤ አሁንም እንወዳለን፤ ወደፊትም እንወዳለን። ይህ በደማችን ውስጥ ያለና መቼም ቢሆን ከልባችን ሊወገድ የማይችል ነገር ነው፤” ብለው እንደነበር አስታውሳለው ።
በአንድ ወቅትአንድ ዘጋቢ የኢትዮጵያን ባንዲራ በሚመለከት ተዘዋውሮ ካናገራቸው የመዲናይቱ ነዋሪዎች አንዱ፥ “እኛ አገራችንን የምንወደው ወያኔዎች ስለነገሩን አይደለም። እሱማ ባንዲራችንን ባጥላሉበት ዘመንም አገራችንን እንወድ ነበር፤ አሁንም እንወዳለን፤ ወደፊትም እንወዳለን። ይህ በደማችን ውስጥ ያለና መቼም ቢሆን ከልባችን ሊወገድ የማይችል ነገር ነው፤” ብለው እንደነበር አስታውሳለው ።

ሰንደቅ ዓላማችን እንዳገራችን እራሷ ባለታሪክ ናት። ሰንደቅ ዓላማችን፣ እነሱ እንዳሏት “ጨርቅ” ብቻ ሳትሆን ስንት ደም የፈሰሰባት ወድቃ የተነሳች ልዩ የታሪካችን መዘክርና የማንነታችን ማብሰሪያ ሰንደቅ ናት።
አቶ ኦባንግ ሜቶ እና አቶ አብዱላሂ ሁሴን በኖርዌይ ኦስሎ ከኢትዮጵያውያንና ከኖርዌጅያን ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ
አቶ ኦባንግ ሜቶ የአዲሲትዋ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፓሬዝዳንትና አቶ አብዱላሂ ሁሴን የኦጋዴን ክልል ፕሬዝዳንት አማካሪ የነበሩና በክልሉ የሚደረገውን የህዝብ ጭቆና፥ እንግልት፥ ግድያ የሚያሳዪ ወደ መቶ ሰአታት የሚደርሱ የቪዲዮ ማስረጃዎችን ይዘው በመሰደድ ለአለም ህዝብ እያጋለጡ ያሉና በአሁኑ ሰአት በስዊድን ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት አጊንተው የሚኖሩ ሲሆን ከማርች 6 እስከ ማርች 7 ,2014 በነበራቸው የኖርዌይ ቆይታቸው ከተለያዩ የኖርዌይ ባለስልጣናት ጋር በሃገራችን ውስጥ ስለሚደረገው የሰብአዊ መብት ረገጣ በማስረጃ በተደገፈ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፥ በመቀጠልም በነበራቸው ቆይታ ስፖንሰር አድርገው ባመጧቸው Solveig Syversen በተባሉ አክቲቪስትና እንዲሁም Frontline Club Oslo በተሰኘ ድርጅት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኖርዌጂያንና ኢትዮጵያውያን Filmenshus በተባለ ቦታ ተገኝተው በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ በማስረጃ በተደገፈ ለህዝብ ያቀረቡ ሲሆን ከታዳሚውም በተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፥ ማርች 7/2014 የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አጋጣሚውን በመጠቀም በጠራው አስቸኴይ ስብሰባ አቶ ኦባን ሜቶ እና አቶ አብዱላሂ ሁሴን ከኢትዮጵያውያኑ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ያረጉ ሲሆን በቀጣይም በሃገራችን እየተደረገ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት፥ ግድያ፥ እስራት ለማስቆም ምን መሰራት አለበት
Friday, October 11, 2013
የተሞሉትን የሚተነፍሱ ጠቅላይ ሚኒሰትር – JONAS TAMERU ( OSLO NORWAY )
ለሁለት አስርተ አመታት በኢትዮጲያና በህዝቦቿ ላይ ነግሶ በማን አለብኝነት አድራጊ ፈጣሪ ሆኖ በሁሉም ያገሪቱ አቅጣጫዎች ሰላማዊውን ህዝብ ለሞትና ለስደት እንዲሁም ለእስር ሲዳርግ የነበረው አምባገነኑ የህውሃት ዘረኛ ቡድን የመለስ ዜናዊ ሞት ተከትሎ በይስሙላ ምርጫ ያስቀመጠው አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የዚሁ ዘረኛ ቡድን ደቀ መዝሙር ሆኖ በነሱ በመቃኘት ተፈጥሮአዊ ባህሬያቸውን ወርሶ አሁንም በሃገራችን ስርዓቱ ካለው እኩይ ተፈጥሯዊ ባህሪ አንፃር የናፈቅነውንና የተመኘነውን ነፃነትም ሆነ ለውጥ ሳይመጣ እነሆ ሌሎች ንፁሃን ሲገደሉና ሲሰደዱ እንዲሁም ሲታሰሩ አየን ሰማን፡፡
ለብዙሃን ዜጎች ህይወት መጥፋት፣ መሰደድና በየእስር ቤቱ መታጎር ተጠያቂ የሆነው አምባገነኑ የወያኔ ቡድን እንዲሁም ስርዓቱ በተለይ ሃገር ሲያፈርሱ፣ ሲመዘብሩና ደሃውን የህብረተሰብ ክፍል ሲየፈናቅሉና በችጋር ሲቆሉ የነበሩት የህወሃት መስራቾች በዘፈቀደ ባገኙት አጋጣሚ እዚህ ምስኪን ህዝብ ላይ አፋቸውን ማላቀቃቸውን መዘባበታቸው የተለመደ ቢሆንም የወያኔ ጠ/ሚንስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በተለያየ አጋጣሚ በስርዓቱ መገናኛ ቡዙሃን ቀርበው የሚሰጡት አስተያየትም ሆነ የሚናገሩት እጅግ የወረደና ስነምግባር የሌለው ዲስኩር ሰውየው በራሳቸው ሳይሆን ስርዓቱ እንደፈለገ እንደሚዘውራቸው ፍንትው አርጎ የሚያሳይ ነው፡፡
Monday, July 8, 2013
Clear and Present Danger
[Jonas Tameru-Oslo]
It has been more than two years since Ethiopia announced its plans to construct the biggest hydro- electric dam in Africa, the Grand Renaissance Dam on the river Nile. This controversial project has from its initiation been a topic of debate among the three countries affected most by this project. Egypt, Sudan, and Ethiopia. Now however after the second year of construction came to an end, Ethiopia has commenced with the route diversion of the Nile in order to be able to begin the actual construction of the dam structure.
Thursday, June 6, 2013
አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት
ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-
1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣
2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።
ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በአባይ ጉዳይ ላይ ዛሬ ደግሞ…
ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

Subscribe to:
Posts (Atom)